ብርሃን ዘታቦር ደ/ታቦር ፬ መጻሕፍተ ጉባኤ ሚዲያ Birhan ze Tabor

ይህ ሚዲያ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/ደ/ጎ/ሀ/ስብከት መቀመጫውን ብሉይ ተክሌ ሐዲስ ተክሌ እና አለቃ ተክሌ ወንበር ይነገርባት በነበረ ደ/ታቦር ደ/ል/መድኃኔዓለም ቤ/ክ/ ያደረገ የዐራቱ ጉባኤያት ትርጓሜ መጻሕፍት ምስክር ጉባኤ ቤት የ-ብዙኃን መገናኝ የመረጃ ትስስር ገጽ ነው። በመሆኑም ሃይማኖታዊ ትምህርቶች፣ምክረ አበው፣ትምህርታዊ የቀጥታ ስርጭት፣የተለያዩ መልእክት የያዙ ቪዲዮዎች የሚለቀቁበት፣ የሚማሩበትና የሚከታተሉበት ቻናል ነው፡፡ ይህም 
ጉባኤ ቤቱ በብጹእ አቡነ ሚካኤል ብርቱ ጥያቄ በክቡር ጌታው የኔታ ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ የልጃቸው(የምክትል መምህር) ልዩ ስጦታ በብጹእ አቡነ ኤልሳዕ (በረከታቸው ይድረሰን) የመሠረት ድንጋይ አስቀማጭነት በ2011 ዓ/ም ወርኀ የካቲት በየኔታ መምህረ መምህራ በጽሐ ዓለሙ ላቀው ምስክር መምህርነት እየተመራ የተመሠረተ ተቋም ሲሆን፤
ትልቅ ርዕይ እና እሩቅ እሳቤ ባላቸው የጉባኤ ቤቱ ምስክር መምህር አቅጣጫ ሰጭነት ዓለም አቀፍ የልህቀት  ማዕከል ለመሆን የሚያስችል ሥራዎችን እየሠራ ሲሆን ከሥራዎቹም፡-  ልዩ ፍላጎት ላላቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች፣ በማረሚያ ቤት ለታራሚዎች፣ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር፣ ለአካባቢው ማኅበረሰብ በተለይ በወጣቶች፣ ለመንግስትና ግል  ሰራተኞች፣ለኢትዮጵያ ጠረፋማ ቦታዎች ላሉ ምእመናን፣ልዩ ልዩ ሙያ ላላቸው ምዕመናንን ለዓይነ ስውራን፣ ለምስክር ጉባኤያት እና ሌሎች የአብነት ት/ቤቶች፣ ለማኅበረ ካህናት እና ለመምህራን፣ ለዓለም አቀፉ የህብረተሰብ ክፍል፣ ለገዳማዊ ሕይወትና መሰል አካላትን ኢላማ አድርጎ በመንቀሳቀስ ተደራሽነቱን ለማስፋት ታሳቢ ያደረገ  ነው፡፡
ኢ/ንግድ ባንክ1000278305701 አባይ ባንክ2131118555328018 አሐዱ ባንክ1826311 ደ/ታቦር 4ቱ ጉባኤያት