MEKDELA መቅደላ

Mekdela_መቅደላ
መቅደላ ካንድ ለብዙኃን የተሰኘ የሕዝብ መገናኛ የዐማራ ህልውና ድምፅ ነው። መቅደላ ዳግማዊ ዐፄ ቴዎድሮስ ለኢትዮጵያ አንድነት ዘላቂነት፣ለአገሪቱና ለሕዝቡ ክብርና ነፃነት ፀንቶ መዝለቅ የራሳቸውን ሕይዎት በጀግንነት የሰውበት ታሪካዊ አምባ ነው። መቅደላ የአንድነት፣ የጀግንነት፣ የቆራጥነትና የክብር መስዋዕትነት መታወሻ ሕያው አምባ ነው።
ይህ አምባ ኢትዮጵያ በአካባቢ የጦር አበጋዞች ተከፋፍላ አንድነቷ ትል የበላው አገዳ በነበረበት ወቅት የአንድነትና የዕድገት ቀናዒ የነበሩት ዳግማዊ 0ፄ ቴዎድሮስ የጦር አበጋዞችን በማንበርከክ የዘመናዊውን አንድነት ጉዞ መሠረት የተጣለበት ታሪካዊ ቦታ ነው። እኛም ይህን የብዙኃን መገናኛ መቅደላ ብለን የሰዬምነው ፤ዛሬ አገራችን ከዚያን ጊዜው በከፋ መልኩ የኢትዮጵያ አንድነት በአገር በቀል ፀረ-ዐማራና ፀረ አንድነት ቡድኖች ከፍተኛ ችግር ውስጥ የገባችበት በመሆኑ፤ ይህ የቁልቁለት የመበታተን ጉዞ ለመግታት፣ ለዐማራው ህልውና እና ለኢትዮጵያ አንድነት በቆጠኝነት ለቆሙ፣በዚህም የተነሳ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ዓለም አቀፍ ወንጀል ሰለባ ለሆነው ዐማራ፤ እንዲነቃ፣ እንዲሰባሰብ እና ለህልውናው ራሱ ዘብ እንዲቆም የሐሳብ ስንቅ ፣ የመረጃ ልውውጥ ቋት የግፉአን ድምፅ ለመሆን ነው።