አሐደ ለከ ወአሐደ ለሙሴ
Автор: ሠናይ ዜማ
Загружено: 2025-08-14
Просмотров: 416
ደብረ ታቦር
አሐደ ለከ ወአሐደ ለሙሴ ወአሐደ ለኤልያስ ንግበር ማኅደረ።
አንዱን ለአንተ፣ አንዱን ለሙሴ፣ አንዱንም ለኤልያስ የማደሪያ ዳስ እንሥራ።
ከሁሉ በፊት ልዑል እግዚአብሔር በቸርነቱ ለበዓለ ደብረ ታቦር እንኳን አደረሰን!
በዓለ ደብረ ታቦር በወርኃ ክረምት ነሐሴ 13 የሚውል ነው። ደብረ ታቦር ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን የገለጸበት፣ አብ በደመና ሆኖ “የምወደው፣ የማፈቅረው ልጄ ይህ ነው” ብሎ ለሦስተኛ ጊዜ የመሠከረለት ነው።
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቀደምት ነቢያት ነቢይ ሙሴንና ነቢይ ኤልያስን፣ ከሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስን፣ ቅዱስ ያዕቆብን፣ ቅዱስ ዮሐንስን አምጥቶ ብርሃነ መለኮቱን የገለጸበት ነው።
ደብረ ታቦር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ በደማቅ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት ይከበራል።
የበዓሉን ዋና ምሥጢር የሚገልጽ መዝሙር አቅርበናል። ተከታተሉት፣ አስተያየት ስጡ፣ ዝም አትበሉ! ባለቤት ናችሁ፣ ተሳተፉ። ቻናሉ ምን ምን መጨመር እንዳለበት ጻፉ። ሰብስክራይብን፣ ላይክን፣ ኮፒ ሊንክን ማድረግን አስታውሱ። መልካም በዓል!
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: