ስልጤ ወራቤ እንግዶቿን እየተቀበለች ነው ❤
Автор: ስልጤ ሳንኩራ ሚዲያ
Загружено: 2025-12-06
Просмотров: 495
አርሂቡ የምጠብኝ - እንኳን ደህና መጣችሁ!!
የ20ኛውን የኢትዮጵያ ብሄርብሄረሰቦች በዓል ለማክበር ወደ ክልላችንና ወደ ስልጤ ዞን የሚመጡ እንግዶችን በድምቀት ለመቀበል የስልጤ ዞን ከፍተኛ አመራር አካላትና የወራቤ ከተማ የማህበረሰብ ክፍሎች እንዲህ ባማረ ሁኔታ መሰናዷቸውን አጠናቀው በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።
በመርሃ ግብሩ ላይ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ዘይኔ ቢልካ፣ የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪና የዞኑ ብልጽግና ቅ/ጽ/ቤት ዋና ሀላፊ ክብርት ወ/ሮ ነዒማ ሙኒር፣ የስልጤ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪና የዞኑ ግብርና መምሪያ ሀላፊ አቶ ሙበራ ከማል፣ የወራቤ ከተማ ከንቲባ አቶ ያሲን ከሊል፣ የዞንና የወራቤ ከተማ አመራር አካላት እንዲሁም ልዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን ''ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ቃል በሃገር አቀፍ ደረጃ ህዳር 29 ቀን 2018 በማዕከላዊ #duet #habesha #love #motivation #lifeisbutadream #nothingimposibleinthisworld #haveitoldyoulatelythatiloveyou ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ የሚከበር ሲሆን ከዋናው መርሃ ግብር በፊት ወራቤን ጨምሮ በሁሉም የክላስተር ከተሞች ልዩ ልዩ ዝግጅቶችና መርሃ ግብሮች መከናወናቸውን ቀጥለዋል።
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: