የ2017 የዩንቨርሲቲ መግቢያ ፈተና
Автор: Muja Mercury
Загружено: 2025-05-17
Просмотров: 267
የ2017 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ፈተናን በወረቀት ለሚፈተኑ ተፈታኞች
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከቀድሞው የተሻሻለ የመልስ መስጫ ወረቀት ለተፈታኞች ምቹ በሆነ ዲዛይን በአዲስ መልክ አዘጋጅቷል፡፡ ስለሆነም ተፈታኞች ማድረግ ስለሚገባቸው ጉዳዮች ማስገንዘብ በማስፈለጉ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
✅ተፈታኞች ማድረግ ያለባቸው ነገሮች
👉ክረምት ከመሆኑ አኳያ በሚፈጠር እርጥበት፣ የምትፈተኑበት ጠረጴዛ ላይ ባለ ፈሳሽ ነገርም ይሁን በሙቀት በሚፈጠር የእጅ ላብ ወረቀቱ እንዳይረጥብ እና እንዳይቀደድ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው።
👉ሙሉ ስማቸውን የሚፈተኑትን የት/ት ዓይነት እና የተማሩበትን ት/ቤት በcapital letter ሊነበብ በሚችል መልኩ በተቀመጠው ጠቋሚ መሰረት ነጭ ቦታው ላይ ብቻ ይፃፉ፡፡ የሚጽፉትን ከአድሚሽን ካርዳቸው ጋ ማግኘት ይችላሉ።
👉የመፈተኛ መለያ ቁጥራቸውን(ከአድሚሽን ካርዳቸው) የት/ቤት መለያ ቁጥራቸውን(ከአድሚሽን ካርዳቸው) የሚፈተኑትን የጥያቄ ወረቀት መለያ ቁጥር(hጥያቄ ወረቀቱ )እና የት/ት ዓይነቱን መለያ ቁጥር ከአድሚሽን ካርዳቸው ወይም ከጥያቄ ወረቀቱ) በመውስድ በትክክል በቦታው ላይ መፃፍ እና በተፃፈው ትይዩ ወደታች የፃፉትን ቁጥርበተሰጠው የአጠቋቆር መግለጫ መሰረት በትክክል ሙሉ ክቡን ማጥቆር ግዴታ ነው።
👉ፈታኙ የፃፈውን እና ተፈታኙ ፅፈው ያጠቆሩትን የጥያቄ ወረቀት መለያ ቁጥር ተመሳሳይመሆኑን ማረጋገጥ።
👉በሚፈተኑት የት/ት ዓይነት የጥያቄ ቁጥር ብዛት መሰረት እና በተሰጠው የአጠቋቆርመግለጫ መሰረት ከአራቱ አማራጮች ውስጥ መልስ ነው ብለው ያመኑበትን አንድ ፊደል
👉መልሱን ሲያጠቁሩ ተሳስተውም ይሁን መልስ ቀይረው ለማስተካከል ከፈለጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን መልስ እርሳሱ እስኪለቅ ድረስ በደንብ ማጥፋት ግዴታ ነው።
🙅♂️ተፈታኞች ማድረግ የሌለባቸው ነገሮች
👉ፈሳሽ ያለበት ነገር ላይም ይሁን እርጥበት ያለበት ቦታ ላይ የመልስ ወረቀቱን ማስነካት ወይም ማስቀመት በፍጡም የተከለከለ ነው።
👉መፃፍም ይሁን ማጥቆር ከሚገባቸው ቦታ ውጪ የመልስ ወረቀቱ detect mark guide (5ቱ ክቦች)፣ ከመስሪያ ቦታው ውጪ ባሉ አራቱም ህዳጎች እንዲሁም ከመልስ ወረቀቱ ጀርባ ላይ በምንም አይነት መልኩ የእርሳስም ይሁን የሌላ ነገር ምልክት መተው በፍፁም የተከለከለ ነው።
👉ከአንድ በላይ መልስ ማጥቆር
👉ምንም መልስ ሳያጠቁሩ ማለፍ
📌ማጠቃለያ
👉መኮረጅም ይሁን ማስኮረጅ ሙሉ ውጤትን እስከመሰረዝ ድረስ ያስቀጣል።
👉ከአንድ በላይ መልስ ማጥቆር ውጤት አያሰጥም።
👉ምንም መልስ አለማጥቆር ውጤት አያሰጥም።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት                
 
                Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
- 
                                Информация по загрузке: