ከቅዱስ ገብርኤል ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የቀረበ የአብሮነት ጥሪ
Автор: Saint Gabriel Catholic Church
Загружено: 2025-08-19
Просмотров: 242
ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።
ለብዙዎች በቤቱ መገኘት ደስታን የሚፈጥረው ቁምስናችን ቅዱስ ገብርኤል ጥሪውን ያስተላልፋል።
ግንባታው በ 1931 ዓ.ም በኮንሶላታ ካቶሊክ ሚሲዮናዉያን ተጀምሮ በተለያዩ ተግዳሮቶች መሠራት ሳይችል፤ በሰኔ 19 ቀን 1958 ዓ.ም በዕለተ ገብርኤል ተጠናቆ በብፁዕ አቡነ አስራተ ማሪያም የምሩ ተባርኮ ላገልግሎት የበቃውና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ውስጥ የሚገኘው የቅዱስ ገብርኤል ቁምስና።
ቁምስናው እስካሁን ወደ 20 በሚጠጉ ካህናት በቆሞስነት አገልግሎቱን ለምዕመናን ሲያደርስ ቆይቷል።
ቤተክርስቲያናችን በአሁኑ ወቅት በዕድሜ ብዛትና በተለያዩ የተፈጥሮ ዕክሎች ምክንያት ተገቢውን የስርዓተ አምልኮ አገልግሎት ለመስጠት እየተቸገረ ይገኛል። በመሆኑም ይህንን የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ ለማነጽ ሁላችንም በጋራ እንድንነሳ በቤቱ ባለቤት በእግዚአብሄር ስም እንጠይቃለን።
እግዚአብሔር አገልግሎታችንና ልግስናችንን ይባርክ
የቅዱስ ገብርኤል ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ቆሞስ ምእመናን ምክር ቤትና ምዕመናን።
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: