አንተ ፈጥረኸናል
Автор: Abba Dawit Wubishet - አባ ዳዊት ውብሸት
Загружено: 2025-11-03
Просмотров: 86
ይህ የመዝሙር ሥራ፣ "ኑዛዜ" የተሰኘው የቅዱስ አውጎስጢኖስ መጽሐፍ ከእንግሊዘኛ ወደ አማርኛ በዘካሪያስ ደበበ ተተርጉሞ በመጽሐፉ ምረቃ ጊዜ እንዲዘመር የተዘጋጀ ነበር፡፡ የግጥሙ ይዘት ሙሉ በሙሉ ከ "ኑዛዜ" መጽሐፍ የተወሰደ ሲሆን የሙዚቃው ቅንብር በአብይ ወልደማርያም የተሰራ ነው፡፡
This song was prepared for the launching of the Amharic translation of the Confession of St. Augustine. The translation from English to Amharic was done by Zecharias Debebe. The verses of the song are based on St. Augustin's Confessions, as referenced below. The chorus is from St. Augustin's well-known prayer- Our heart is restless until it rests in Thee.
አንተ ፈጥረኸናል
አንተ ፈጥረኸናል ጥበበኛ ጌታ
ልባችን በአንተ እስክታገኝ ፋታ
ዕረፍትን ትሻለች ዘወትር ተጠምታ (2ቴ) ከኑዛዜ ምዕራፍ 7
በሌላ ተስፋ አድርጋ አንተን ለዘነጋች
እዚህና እዚያ ብላ ከርታታ ለሆነች
ጠማማውን መንገድ ደፍራ ለያዘች ብኩን ነፍስ
አንተ አለህላት ዕረፍት ምትሆናት ፈውስ
ቅርብነትህን እንጂ ጉስቁልና እንዳትለብስ (2ቴ)ከኑዛዜ ክፍል 1. ምዕራፍ 7
ፍጥረታት እንኳን ሳይቀሩ ሕጉን ተከትለው
እሣትና ድንጋይም ስፍራቸውን አውቀው
ዘይትና ውሃም እኮ ቦታቸውን ይዘው
በተገቢው መልኩ የማይገኙ ሆነው
ሰክነው የማይቆዩ ዕረፍት የለሽ ናቸው (2ቴ) ከኑዛዜ ክፍል 6. ምዕራፍ 8
እንደ ድንጋይ መክበዳችን ሆኖ በአንተ ክብር
እንደ እሣት መንደዳችን ሆኖ በአንተ ፍቅር
ወደ ላይ ከፍ ብንል ብንቀልጥ በውስጣችን
መንገድህ ነውና የአንተ ሰላማችን
ብቻ አንተ መልካም ነህ ደስታ ማረፊያችን (2ቴ) ከኑዛዜ ክፍል 13. ምዕራፍ 8
ጥንታዊም አዲስም የሆንክ ኦ ውበት ውበት
ምነው አንተን ለማፍቀር ባልነበር መዘግየት
ዘገየስ በከንቱ ፍጹም ከቶ ባለማወቅ
ውስጣችን እያለህ ሌላ ጋር ስንናፍቅ
ጠርተህ ስተነፍስ መዓዛህን እንድናደንቅ (2ቴ) ከኑዛዜ ክፍል 10. ምዕራፍ 27፡38
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: