የኢትዮ ግሪን ሞቢሊቲ 2025 ኢግዚቢሽን በአፍሪካ ኮንቬንሽን ተከፈተ
Автор: Temar Lije
Загружено: 2025-12-28
Просмотров: 45
የኢትዮ ግሪን ሞቢሊቲ 2025 ኢግዚቢሽን በአፍሪካ ኮንቬንሽን ተከፈተ።
ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ እየገነባች ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 18፣ 2018 የኢትዮጵያ ብልጽግና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማትን ታሳቢ ያደረገ እንዲሆን እየተሰራ ነው አሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ።
በኢትዮጵያ ብክለት ቀናሽ እንቅስቃሴ 2025 ኤግዚቢሽን እና ፎረም ተጀምሯል፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንዳሉት÷ የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (ኮፕ2032) እንድታዘጋጅ የተመረጠችው ኢትዮጵያ ሰፋፊ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስራዎችን እያከናወነች ነው።
በኢትዮጵያ የተሟላ ለውጥ እና ብልጽግናን ለማምጣት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው÷ ይህ ዘላቂ ልማት እና ለውጥ አረንጓዴ ኢኮኖሚን ታሳቢ ያደረገ እንዲሆን ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
የአየር ንብረት መለዋወጥ የከተሞች መጨናነቅ እና ዝቅተኛ የኃይል አቅርቦት የልማት ፈተናዎች መሆናቸውን ጠቅሰው÷ ኢትዮጵያ ችግሮቹን በመረዳት መፍትሄ ለመስጠት ከጠረጴዛ ተኮር ወደ ተግባር ተኮር ስራ መሸጋገሯን አብራርተዋል፡፡
በነዳጅ ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ እንዲሁም የልማት ስራዎችን ከፀሐይ፣ ከሃይድሮ ኤሌክትሪክ እና ከነፋስ ኃይል ልማት ጋር ለማስተሳሰር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: