ለኤርትራ መንግስት የ60 ቀን ገደብ ተሰጠ//የተደረገው የ26 ዓመታት ትግል- የቀይ ባሕር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት
Автор: Ahadu News & Politics
Загружено: 2025-12-27
Просмотров: 740
የኤርትራ መንግሥት በደናከል አካባቢ በቀይ ባህር አፋር ሕዝቦች ላይ እየፈፀመ ያለውን መጠነ ሰፊ ፣ ስልታዊ ፣ መንግሥታዊ መር የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እንዲሁም የዘርማጥፋት ወንጀል ተባብሶ በመቀጠሉ የቀይ ባህር የአፋር ሕዝቦች የሚደርስባቸው መከራን ለመከላከል ፣ የአለም አቀፍ ብዙሃን መገናኛ ድምፅ እንዲሆኑ እና አህጉራዊና አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ተቋማት ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት ትኩረት እንዲሰጡ እንዲሁም የኤርትራ መንግሥት ላይ ህጋዊ ፣ ዲፕሎማሲያዊ ፣ ሰብዓዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እንዲወሰዱ እና ተፅዕኖ እንዲያሳድሩ የድርጅቱ አመራሮች ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የኤርትራ መንግስት በአካባቢው ከህግ እና ከፍርድ ውጭ ግድያዎች እና ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ፣ ያለ ፍርድ ማሰር እና ማሰቃየት ፣ የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ ፣ በግዳጅ ማፈናቀል ፣ ፆታዊ ጥቃትን የአገዛዙ የአፈና መሳሪያ አድርጎ መጠቀም ፣ ከሀገሪቱ ፖለቲካዊ አስተዳደር ማግለል ፣ የቀይ ባህር አፋር ሕዝብን ማንነትና ባህል ማጥፋት ፣ ኢኮኖሚያዊ መብቶቻችን መጣስ እና መሰል የመብት ጥሰቶች መፈፀማቸው ተጠቅሷል።
በዚህም ድርጅቱ ኤርትራ አባል የሆነችበትን የአፍሪካ ቻርተር የሕዝቦች መብት ኮንቬንሽን ላይ እውቅና ያገኙ 26 የሰብዓዊ መብት ድንጋጌዎችን በመጣሱ ለአፍሪካ የሰብዓዊ እና ሕዝቦች መብቶች ኮሚሽን ሰኔ 04/2025 የክስ አቤቱታ 122 ገፅ ከሙሉ ማስረጃዎች ጋር አቅርቧል፡፡ በዚህ ልዩ ቃለ ምልልስም ድርጅቱ በቀይባህር አፋር ህዝብ ላይ የኤርትራ መንግስት እያደረሰ ነው ስላለው የሰብአዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብት ጥሰት ገጽታ፤ በስደት ወደ ኢትዮጵያ የገቡት ከ300.000 መቶ ሺህ በላይ ዜጎች ሁኔታ፡ የደርጅቱን የጦር ሀይል አደረጃጀት፤ የመገንጠል ጥያቄውን እና ኢትዮጵያ የወደብ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ ለምትሰራው ስራ የሚሰጠውን ድጋፍ በተመለከተ ትኩረት ተደርጓል ሙሉ ቃለ ምልልሱን ተከታዩን ሊንክ በመጫን ይከታተሉ ፡፡Eritrea, Ethiopia,RedSea Afar, RSADO, Assab Port, IsaiasAfwerki, Human Rights, AfricanCommission, Abdu Sheik, Nesreddin Ahmed,EritreanOpposition, Dankalia, Horn of Africa Politics,አሰብ, ኤርትራ, ኢትዮጵያ, ቀይ ባህር, አፋር, አብዱ ሼክ, ነስረዲን አህመድ, የኤርትራ ተቃዋሚዎች #Eritrea#Ethiopia #RedSea #Afar #Assab #HumanRight
#RSADO #Africa
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: