የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት አዋጅ በአራት ዓመት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ተሻሻለ
Автор: Ethiopia Insider
Загружено: 2025-05-29
Просмотров: 2155
በውጭ ሀገር ለስራ የሚሰማሩ ኢትዮጵያውያንን የሚመለከተው አዋጅ፤ ከአራት ዓመት በኋላ በድጋሚ ማሻሻያ ተደረገበት። የአዋጅ ማሻሻያው በውጭ ሀገር ለስራ የሚሰማሩ ዜጎች “መብታቸው፣ ደህንነታቸው እና ክብራቸው በዘላቂነት መጠበቁን ለማረጋገጥ” “እንዲያስችል ሆኖ የተዘጋጀ ነው” ተብሏል።
በ2008 ዓ.ም የወጣው “የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ስምሪት አዋጅ” ሰራተኛን በውጭ ሀገር ለስራ ማሰማራት የሚቻለው፤ “በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት እና በተቀባይ ሀገር መካከል የሁለትዮሽ ስምምነት ሲኖር ብቻ እንደሆነ” የሚገድብ ድንጋጌ ነበረው። በ2013 ዓ.ም. የጸደቀው የዚህ አዋጅ ማሻሻያ በበኩሉ፤ በውጭ ሀገራት “የሰለጠነ የሰው ኃይል” ለሚፈለግበት ስራ ተጨማሪ ሁለት የስምምነት አማራጮችን አካትቷል።
የመጀመሪያው አማራጭ፤ ጉዳዩ በሚመለከተው የኢትዮጵያ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት እና በተቀባይ ሀገር ከሚገኘው አቻ ስልጣን ካለው የመንግስት ተቋም ጋር “የሁለትዮሽ ስምምነት” ወይም “መግባቢያ ሰነድ” ሲኖር ሰራተኛን ማሰማራት እንደሚቻል ይፈቅዳል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተመሳሳይ ስምምነት በውጭ ሀገር ከሚገኝ “እውቅና ካለው አሰሪ ኩባንያ” ጋር ከፈጸመም፤ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን መላክ እንደሚቻል በአዋጁ ማሻሻያው ተደንግጓል።
🔴 ዝርዝር ዘገባውን በጽሁፍ ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2025/16038/
--------------------------------------------------------------------------------------------------------------------
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ http://ethiopiainsider.com
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
ቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopiaInsiderNews
ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: