ሐጌ: ቤተ መቅደስ //እንዳሻው ነጋሽ// Haggai: Temple// Endashaw Negash
Автор: Endashaw Negash
Загружено: 2021-01-03
Просмотров: 1231
ነቢዩ ሐጌ በድኅረ ምርኮ ካገለገሉ ነቢያት መካከል አንዱ ሲሆን የመልእክቱ ትኩረት ሕዝቡ ያቋረጠውን የቤተ መቅደስ ሥራ እንዲቀጥሉ ማድረግ ነው። የመጽሐፉ ማእከላዊ ሐሳብ ቤተ መቅደስ ነው። ለሰባ ዓመታት በምርኮ የቆየው ሕዝብ በሦስት ዙሮች ከምርኮ የተመለሰ ሲሆን በመጀመሪያው ዙር መሪ በዘሩባቤል መሪነት የቤተ መቅደስ ሥራ ከጀመሩ በኋላ ከገጠማቸው ተቃውሞ የተነሣ የእግዚአብሔርን ቤት ሥራ አቋርጠው ወደ ራሳቸው ቤት ዞረው ነበር። በዚህ ወቅት እግዚአብሔር ነቢዩ ሐጌን እና ዘካርያስን በመላክ ለሕዝቡ ተናግሯል። ሐጌ አራት መልእክቶችን የተናገረ ሲሆን አራቱም መልእክቶች የተሰጡበት ጊዜ በዝርዝር ቀርቧል (1÷1፤ 2÷1፣ 10፣ 20)። ከምርኮ የተመለሰው ሕዝብ ቅድምያ ሊሰጠው የሚገባውን ነገር ቸል በማለት የሚጠበቅበትን ኀላፊነት በአግባቡ ባለመወጣቱ ራሱን፣ ሌሎች ሕዝቦችን እና ተፈጥሮን ጭምር ጎድቷል። ሕዝቡ የእግዚአብሔር ቤት ሥራ ቸል በማለቱ በብዙ ለፍቶ በጥቂቱ ማስገባቱ፣ በልቶ አለመጥገቡ፣ ጠጥቶ አለመርካቱ እና ልፋቱ ሁሉ ከንቱ ድጋም መሆኑ ተገልጽዋል። ይህ ብቻ ሳይሆን ከእነርሱ የተነሣ ሰማያት ጠልን እንደ ከለከሉና ምድሪቱም ፍሬዋን እንደ ከለከለች ተነግሯል። የእግዚአብሔር ሕዝብ ውድቀት የሌሎችን ውድቀት የሚያስከትል ነው። ይህቺን አጭር ቪድዮ በመመልከት የመጽሐፉን ማእከላዊ ሐሳብ መገንዘብ ይቻላል።
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: