በምን እንላያቸው? የሞች ጋር የነበረን ጣፋጭ ቆይታ ክፍል 2
Автор: DINK HAGER ድንቅ ሀገር
Загружено: 2024-12-07
Просмотров: 1117
የም ዞን
. . . በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ከሚገኙ የዞን መዋቅሮች ውስጥ አንዷ ናት ፡፡ በተፈጥሮ ውበት የታደለች ምድሪቱ የተዘራባትን የምታበቅል ህዝቦቿ ሰው አክባሪ እንግዳ ተቀባይ ናቸው ፡፡ አብዛኛው የዞኑ ሕዝብ በግብርና የሚተዳደር ሲሆን እንደ ገብስ፣ ጤፍ፣ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ያሉና የተለያዩ የአገዳና የመኽር ሰብሎች ፣ ፍራፍሬና አትክልት በሰፊው በማምረት ይተዳደራሉ ፡፡
በሚያስገርም እና በሚያስደንቅ ሁኔታ በዞኑዋ ላይ ልመና የሚባል ነገር ከቶ አይታሰብም ፡፡ ለዚህም ዋና ምክንያቱ ደግሞ ማህበረሰቡ እርስ በእርስ የመረዳዳት፤ የመተሳሰብ ባህልን ሲወርድ ሲዋረስ ከጥንት አባቶቹ በመረከብ አስጠብቆ በመቆቱ ነው ፡፡
ይህ አስደናቂ ስፍራ የም ዞን ሲሆን ዋና ከተማዋ ሳጃ አዲስ አበባ ጅማ በሚወስደው ዋና የአስፋልት በ239 ኪ/ሜ ላይ ይገኛል ፡፡
ድንቅ ሀገርም ይህን አስደናቂ ስፍራ በውስጡ ስላሉ ታሪካዊ ፤ ሰው ሰራሽ ፤ ተፈጥሮአዊ መስእቦች በሰፊው ለውድ ተመልካቾቻችን ለማስዳሰስ ከመዲናችን አዲስ አበባ ተነስተን ወደ የም ዞን ሳጃ ከተማ ገሰገስ ፡፡
የየም ማህበረሰብ በጆሮ ከሰማነው በላይ ሰው ወዳድ እንግዳ ተቀባይ መሆኑን በአካል ተገኝተን አስተዋልን በቆይታችን እንግዳ መሆናችንን እስክንረሳ ድረስ ከህፃን እስከ አዋቂ የተለየ እንክብካቤ ሳይለየን በየገባንባቸው ወረዳዎችና ቀበሌዎች ምርጥ ቆይታን አሳለፍን ፡፡
በየም ዞን ቆይታችን አንጋፋውን በለምለም መስክ ላይ ተንጣሎ የሚገኘውን የአንጋሪ ቤተ መንግስትን ጎበኘን ፡፡ የየም ማህበረሰብ የራሱን የአስተዳደር መዋቅር መሥርቶ በነገስታት ይተዳደር እንደነበረ ታሪክ ያወሳል ፡፡ በዚህም መሰረት የጋማ ሥርወ መንግሥት ፤የጌሜሎ ሥርወ መንግሥት እና የሞዋ ሥርወ መንግሥት ተፈራርቀው ያስተዳድሩት ሲሆን የአንጋሪ ቤተ መንግስትም ከ13 ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ የሞዋ ሥርወ መንግሥት መቀመጫ ሆኖ በማገልገሉ እስካለንበት ግዜ ድረስ ቀደምት ውበቱን እንደያዘ የዞኑ መስእብ ሆኖ ተገቢው ጥበቃ እየተደረገለት በክብር ተቀምጧል ፡፡
በዞኑ ቆይታችን በሳጃ ከተማ በቅርብ ርቀት የሚገኘውን ለአይን ማራኪ መንፈስን አዳሽ ልዩ ውበት ያለው የብርብርሳ ፏፏቴን ጎበኘን አያይዘንም በማህበረሰቡ ትልቅ ቦታ የሚሰጠውን ከሳጃ በ32 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በፎፋ ከተማ አቅራቢያ የሚገኝ ከባህር ወለል በላይ 2939 ሜትር ከፍታ ያለው በልዩ ወረዳው ከሚገኙ ተራሮች የቦር ተራራ ትልቁ ስፍራ የሚይዘውን ስፍራ አቀናን ፡፡
ይህ የቦር ተራራ በማህበረሰቡ ዘንድ ትልቅ ቦታ እንዲሰጠው ካደረገው ውስጥ የብሔረሰቡ አባላት በአመት አንድ ግዜ ጥቅምት 17 በአንድነት ወጥተው ከተለያዩ ዕፀዋት መድኃኒት የሚለቅሙበት ስፍራ በመሆኑ ነው በቦር ተራራ ውስጥ ሃገር በቀል እፅዋቶች ብዛት ያላቸው ለመድሃኒትነት የሚያገለግሉ ስራ ስሮች በሰፊው የሚበቅሉበት ነው ፡፡ ማህበረሰቡ ለደን ትልቅ ቦታ ያለው ሲሆን በአመት አንድ ጊዜ ጥቅምት 17 ብቻ ለሚፈልገው አላማ ከመቁረጥ ውጪ ደኖችን አይመነጥርም እፅዋትን አያጠፋም ፡፡
ድንቅ ሀገሮችም በየም ዞን ባሳለፍናቸው ድንቅ ቆይታዎች ይህንና ሌሎችም ታይተው የማይጠገቡ የቱሪዝም ሃብቶችን የማህበረሰቡን የአኗኗር ሁኔታ በስፋት ስንቃኝ ከርመን ለውድ ተመልካቾቻችን ለማስቃኘት በካሜራችን አስቀርተን 2017 ዓ/ም በኢቲቪ ኢንተርቴመንት ለማስቃኘት ወደድን ፡ ፡
ድንቅ ሀገር
ህዳር 2017
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: