🔴👉 [ኪዳነምሕረት በስውር የምታጠምቅበት ገዳም] ደጁን መርገጥ ገነት ያስገባል!!!
Автор: ጊዜ ሚዲያ gize media
Загружено: 2021-01-25
Просмотров: 284553
ደጅሽን የረገጠውን የሲኦልን እሳት አላሳየውም ብሎ ጌታችን ቃልኪዳን የገባባት ምስጢራዊ ገዳም፣ ኪዳነምሕረት በስውር የምታጠምቅባት፣ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት የመረጧት ያድሩባት የነበረ፣ ያልተገለጡ 17 ስውር ፅላት ያሉባት፣ ከስውር ዋሻ ውስጥ የእጣን መዓዛ የማህሌት ድምፅ የሚሰማባታ የበረከት ገዳም እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ ይገኛል ለመሆኑ የት ይሆን የሚገኘው ደጁን መርገጥ በራሱ የሲኦልን እሳት እንዳናይ የሚያደርገን ገዳም?..........ኢትዮጵያ ሀገራችንን የቅዱሳን መናኻሪያ ናት ስንል ብዙዎች አይዋጥላቸውም ነገር ግን እኛ ማለታችንን አናቆምም ሀገራችን ኢትዮጵያ የቅዱሳን ቤት ናት ብዙ ገቢረ ተአምራት የሚደረግባት ሀገረ እግዚአብሔር ኢትዮጵያ ናት ብዙዎች ቅዱሳን ለፀሎት ዋሻነት የመረጧት የሁሉም ቅዱሳን በአታቸው ናት ኢትዮጵያ.... እልፍ ቅዱሳን የተጋድሎ በዓታቸው፣ የጸሎት ዋሻቸው አድርገው የጽድቃቸው መነሻም ሆነ ፍጻሜ አድርገዋታል። ራሱ ጌታችን በአካል እየተገለጠ ታላላቅ ምሥጢራትን የገለጠላቸው ብዙ ቅዱሳን አሉ፤ ክብርት እመቤታችንም እየተገለጠችላቸው ሰማያዊ ምሥጢር የነገረቻቸው እነ ቅዱስ ኤፍሬም፣ እነ አባ ሕርያቆስ፣ እነ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፣ እነ አባ ጽጌ ድንግል እና ሌሎችም በርካታ ቅዱሳን አሉ። ቅዱሳን መላእክት ሰማያዊ ኅብሥትና ጽዋ እያመጡላቸው ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ሲፈትተቱ የነበሩ አሉ፤ የተጋድሎአቸው ብርታት፣ የጸሎታቸው ኃይል የእምነታቸው ጽናት ለጽድቅ ያበቃቸው ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሆኑ ቅዱሳን አሉን ከእነዚህ መካከል ታዲያ ሞትን ሳይቀምሱ እንደነ ሄኖክም እንደነ ኤልያስም የተሰወሩ ብዙ ቅዱሳን አባቶችም መኖራቸው ይታወቃል ይህም ብቻ ሳይሆን ብዙ አስደናቂ ገዳማትም አሏት ጣራው ክፍት ሆኖ ፀሀይና ዝናብ የማያስገባው፣ አፅመ ቅዱሳን በንስር የሚገቡበ፣ እሬሳ የማይበሰብስበት እና አስከሬን የሚሰወርበት እንዲሁም ሌሎችንም በጉያዋ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያቀፈች ምስጢራዊት ሀገር ናት ምን ይሄ ብቻ ዛሬ የምንመለከተውንም ኪዳነምሕረት በስውር እየመጣች የምታጠምቅበትንም ገዳም የያዘች እንጂ::
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: