ዶ/ር እመቤት መለሰ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ሁነው ተሾሙ |DBE |zena |Ethiopiainsider |currentaffairs
Автор: Ethiopia Insider
Загружено: 2024-10-02
Просмотров: 734
በባንክ ኢንዱስትሪው ከ20 ዓመታት በላይ ያገለገሉት ዶ/ር እመቤት መለሰ፤ መንግስታዊውን የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በፕሬዝዳንትነት እንዲመሩ ተሾሙ። ዶ/ር እመቤት የፖሊሲ ባንክ የሆነውን የፋይናንስ ተቋም እንዲመሩ ከመሾማቸው አስቀድሞ፤ ላለፉት አራት ወራት የንብ ባንክ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሆነው ሰርተዋል።
አዲሷ ተሿሚ ልማት ባንክን የመምራት ኃላፊነታቸውን የሚረከቡት ከቀጣዩ ሳምንት መጨረሻ ጥቅምት 1፤ 2017 ጀምሮ መሆኑ ተገልጿል። ይህንኑ የሚገልጽ እና በገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ የተፈረመ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ ልማት ባንክ በዛሬው ዕለት መድረሱን አንድ የባንኩ ኃላፊ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አረጋግጠዋል።
ባንኩ ይህንኑ ለተቋሙ ማኔጅመንት አባላት እና ሰራተኞች በኢሜይል እና በውስጥ ማስታወቂያ ይፋ ማድረጉንም ኃላፊው አስረድተዋል። የሹመት ደብዳቤው ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ በተጨማሪ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፣ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና ለመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር በግልባጭ ተልኳል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
ተጨማሪውን ለማንበብ ይሄን ሊንክ ይጫኑ https://ethiopiainsider.com/2024/14248/
-------------------------------------------------------------------------------------------
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ http://ethiopiainsider.com
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
ቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopiaInsiderNews
ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: