የ“ህገ ወጥ” ኬላዎች ጉዳይ እልባት አለማግኘቱ በፓርላማው ጥያቄ አስነሳ | Ethiopia | trade| transport| checkpoint| Alemu Sime
Автор: Ethiopia Insider
Загружено: 2025-12-17
Просмотров: 208
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፤ በመላው ኢትዮጵያ ያለው የሕገ-ወጥ ኬላዎች ጉዳይ አሳሳቢ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ጉዳይ የተነሳው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ትናንት ማክሰኞ ታኅሣሥ 7፤ 2018 ባካሔደው መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው።
ጥያቄ ካነሱ የፓርላማ አባላት መካከል የሆኑት ወ/ሮ ገነት ጌጤ፤ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቋቋሙ “ህገ-ወጥ” ኬላዎች ‘ህዝቡን እያማረሩ ይገኛሉ’ ብለዋል። በእነዚህ ኬላዎች ውስጥ በአንድ ጉዞ ከ3,500 ብር በላይ የሚጠይቁ መኖራቸውን የጠቀሱት የምክር ቤት አባሏ፤ ይህም በምርትና አገልግሎት ላይ የዋጋ መናር እያስከተለ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
መንግሥት ለምን ይህን ሁኔታ መቆጣጠር እንዳልቻለ የፓርላማ አባሏ ላቀረቡት ጥያቄ፤ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትሩ ዶ/ር አለሙ ስሜ በሰጡት ምላሽ ከቀድሞው አንፃር መሻሻሎች መኖራቸውን ተናግረዋል። ከአንድ ዓመት በፊት “ሀገሩ ሁሉ በገመድ የታጠረ ነበረ” ያሉት ሚኒስትሩ፤ ምንም እንኳን መሻሻሎች ቢኖሩም አሁንም ችግሩ መቀጠሉን አልሸሸጉም።
ለዚህም ዋናው መንስዔ የግንዛቤ ችግር እንደሆነ እና ይህን ለመቅረፍ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን ዶ/ር አለሙ አስረድተዋል። የፓርላማ አባሏን ጥያቄ እና የሚኒስትሩን ምላሽ ከቪዲዮው ይከታተሉ። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
-------------------------------------------------------------------------------------------------
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ http://ethiopiainsider.com
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
ቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopiaInsiderNews
ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: