በትምህርት ሚኒስቴር “ለቀጣዩ ምርጫ ቅስቀሳ የምንጠቀምበትን ሥራ ሰርተናል” - ኢዜማ | Ethiopia | Election | Ezema | Berhanu Nega
Автор: Ethiopia Insider
Загружено: 2025-12-16
Просмотров: 255
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ለቀጣዩ ምርጫ ቅስቀሳ የሚጠቅሙትን ስራዎች መስራቱን አስታወቀ። የፓርቲው መሪ የትምህርት ሚኒስቴርን ለመምራት ባገኙት ዕድል፤ የኢዜማን ፖሊሲ ማስፈጸማቸውንም ገልጿል።
ፓርቲው ይህን ያለው ሰባተኛውን ሀገር አቀፍ ምርጫ አስመልክቶ ዛሬ ማክሰኞ ታኅሣሥ 7፤ 2018 ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ ነው። ኢዜማ በዚሁ መግለጫው፤ ምርጫ በሚካሄድባቸው ቦታዎች በሙሉ እንደሚሳተፍ አስታውቋል።
በዚሁ ወቅት የፓርቲው ብሔራዊ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አቶ ኢዮብ መሣፍንት፤ ኢዜማ በመሪው ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አማካኝነት ያገኘውን የትምህርት ሚኒስቴርን የመምራት ኃላፊነት ተጠቅሞ የፓርቲውን “የትምህርት ፖሊሲ አስፈጽሟል” ብለዋል። ስድስተኛውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ካቢኔያቸውን ሲያዋቅሩ የትምህርት ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፤ መስሪያ ቤቱን ላለፉት አራት ዓመታት መርተዋል።
የኢዜማ መሪ በትምህርት ሚኒስቴር ያለማንም ጣልቃ ገብነት “ያመኑበትን ሲሰሩ ነው የቆዩት” ያሉት አቶ ኢዮብ፤ በዚህም “የምንኮራበትና ለቀጣዩ ምርጫ ቅስቀሳ የምንጠቀምበትን ሥራ ሰርተናል” ሲሉ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ በሌሎች ክልሎችም ፓርቲው በተወካዮቹ አማካኝነት ባገኘው የኃላፊነት ቦታ፤ መሰል ለምርጫ ቅስቀሳ የሚጠቅሙትን ተግባራት ማከናወኑንም አቶ ኢዮብ አክለዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር )
🔴 ዝርዝሩን በጽሁፍ ለማንበብ ፦ https://ethiopiainsider.com/2025/16801/
-----------------------------------------------------------------------------------------------------------------
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ http://ethiopiainsider.com
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
ቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopiaInsiderNews
ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: