ኢየሱስ ታላቅ አምላክ ነህ! || የሀረር አማኑኤል ህብረት መዘምራን
Автор: Tesfa Broadcasting Network | GCME
Загружено: 2025-09-12
Просмотров: 29921
በሀረር አማኑኤል ህብረት መዘምራን የተዘመሩት ዝማሬዎች የየራሳቸው በቂ ምክንያት ያላቸው ወይንም ከምክንያት ጋር የተዘመሩ መዝሙሮች ናቸው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ የዝማሬ ኅብረቱን በልዩ ልዩ ዝማሬዎች ባርኮ ነበር፡፡ በመሆኑም ዘማርያኑ የሚያልፉበትን መንገድ፣ የሕይወት ገጠመኞቻቸውን፣ በስብከት መካከል የተባረኩበትን ቃለ እግዚአብሔር፣ በውስጣቸው የከበደውን መልእክት፣ ወንጌላዊ ኃላፊነታቸውን ሁሉ በዝማሬ በኩል ይወጡ ነበር፡፡
ይኼኛው “ኢየሱስ ታላቅ አምላክ ነህ!” የተሰኘው ዝማሬ እንደሚታወቀው ወደ እግዚአብሔር ህልውና በማድረስ ረገድ ግሩም የሆነ ዝማሬ ነው፡፡ ይህም ዝማሬ ያለፉትን ሃያ ሰባት አመታት በኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ሲዘመር የኖረ ዝማሬ ነው፡፡ በዚህም መዝሙር የኢየሱስን እውነተኛ አምላክነት እና ታላቅነት ማወጅ ግብ ተደርጓል፡፡ በተለይም ቤተክርስቲያኒቱ ያለችበት አካባቢ ይህን የሚጻረር አቋም በከፍተኛ ሁኔታ የሚንጸባርቀበት በመሆኑ፤ የሕይወት ራስ የሆነውን ጌታ እና መድሃኒት የሆነውን አዳኝ አምላክነት ማወጅ ግድ በመሆኑ ይህ ዘመን ዘለል ድንቅ ቅኔ ሊወጣ ችሏል፡፡
#ተስፋ_ለሀረር
#ፅኑ_ተስፋ_አለ!
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: