ስለ ካዎ ጦና ሐውልት ሰዎች ምን አሉ አስደናቅ ንግግር
Автор: Ashu media
Загружено: 2026-01-20
Просмотров: 20
የወላይታ ንጉስ ጦና መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ
**************
በቀደምት የወላይታ ታሪክ 52ኛ እና የመጨረሻው ንጉስ ለነበሩትን ካዎ ጦና መታሰቢያ በወላይታ ሶዶ የተገነባው ሐውልት ተመርቋል።
ሐውልቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላ፣ ሌሎች የዞንና ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የጦና ቤተሰቦች እና የአካባቢው ተወላጆች በተገኙበት ነው የተመረቀው።
የወላይታ ንጉስ ጦና ከ1858 ዓ.ም እስከ 1887 ዓ.ም ድረስ ወላይታን ያስተዳደሩ መሪ ነበሩ፡፡
ንጉስ ጦና ከ131 ዓመት በኋላ ወላይታን አንድ አድርገው ለመሩበት እና በዓድዋ ድል ጊዜ ዘምተው ላበረከቱት ሀገራዊ አስተዋጽኦ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ሐውልት መሠራቱን የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ እታገኝ ኃይለማርያም ተናግረዋል።
የታሪክ ጀግኖችን ማሰብ ለቀጣይ ሥራ የተሻለ ትምህርት ለመውሰድ እንደሚያግዝ የገለጹት ከንቲባዋ፤ የበለጸገች ሀገር ለመገንባት የሚደረገው ጥረት ውጤታማ እንዲሆን በአንድነት እጅ ለእጅ ተያይዞ መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል።
የሐውልቱ ምርቃት ጥንት በሕዝብ እና በመንግሥት መካከል የነበረውን አንድነት እና ጠንካራ የሥራ ባህል እንደሚያሳይ ጠቅሰው፣ ከዚህ ትምህርት በመውሰድ ትውልዱ የራሱን ታሪክ እንዲሠራ ያነሳሳል ያሉት ደግሞ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ናቸው።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላ በበኩላቸው፤ የሐውልቱ ፋይዳ ከምስልነት ያለፈ መሆኑን ጠቅሰው፣ አሁን ያለው ትውልድ በሀገረ መንግሥት ግንባታ የራሱን አሻራ እንዲያኖር በር የሚከፍት ነው ብለዋለል
ሐውልቱ በጦና ጊዜ የነበረውን የጀግንነት ገድል የሚያስታውሱ አመላካቾችን በውስጡ አካቶ መገንባቱ ተመልክቷል።
በአሹ ቶማ
Ashu Media #የወላይታንጉስጦና
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: