ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከሙስሊሞች ጋር በተያያዘ ለተነሱባቸው ቅሬታዎች ምላሽ ሰጡ| Berhanu Nega's full speech | Agena (Gurage Zone)
Автор: Ethiopia Insider
Загружено: 2021-05-22
Просмотров: 49549
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፤ በጉራጌ ዞን አገና ከተማ ለሚገኙ በሺህዎች ለሚቆጠሩ ደጋፊዎቻቸው ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 14፤ 2013 ንግግር አድርገዋል። በአነጋጋሪው የ1997ቱ ምርጫ ወቅት በተመሳሳይ ሁኔታ ለምርጫ ቅስቀሳ ወደ አካባቢው መምጣታቸውን የተናገሩት፤ ዛሬ የተመለከቱት የህዝብ ብዛት በዚያን ጊዜ ከነበረውም የላቀ ነው ብለዋል።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ በዚሁ ንግግራቸው፤ “ጸረ-ሙስሊም” ስለመባላቸው እና “ከወለድ ነጻ የሆነ ባንክን አይወዱም” በሚል ስለሚነሳባቸው ቅሬታ ምላሽ ሰጥተዋል። እንደዚህ አይነት ውንጀላዎች ሁሌም የሚቀርቡባቸው ምርጫ ሲቀርብ እንደሆነ የተናገሩት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፤ “ሌላ ጊዜ ከእኔ ጋር ሰላም ናቸው” ብለዋል።
የገዢው ፓርቲ ሰዎች በኢዜማ ደጋፊዎች ላይ ስለሚያደርሱባቸው ጫና እና የገንዘብ ድለላ መስማታቸውን የጠቀሱት የኢዜማ መሪ፤ እነዚህን ጉዳዩች እንዴት በአግባቡ መመለስ እንዳለባቸው ምክር ለግሰዋቸዋል። “ሰኔ 14 ነው ምርጫው። እስከ ሰኔ 14 ድረስ ሊነኳኳችሁ፣ ሊገፏችሁ፣ ሊያስፈራሯችሁ ይሞክራሉ። እዣ ፈርቶ ሌላ አይመርጥም፤ ይህንን እነግራችኋለሁ” ሲሉ በልበ ሙሉነት ተናግረዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎቻችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ http://ethiopiainsider.com
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር ፦ / ethiopiainsider
#ብርሃኑ_ነጋ #ኢዜማ #ምርጫ_2013
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: