መራጮች እና ተወዳዳሪዎች በሞባይል እና በድረ ገጽ መመዝገብ የሚችሉበት ስርዓት ተዘጋጀ | Ethiopia | Election| NEBE| Ethiopia Insider
Автор: Ethiopia Insider
Загружено: 2026-01-05
Просмотров: 260
በመጪው ጠቅላላ ምርጫ ለውድድር የሚቀርቡ ዕጩዎች እና መራጮች በዲጂታል አማራጭ መመዝገብ የሚችሉበት መተግበሪያ እና የድረ ገጽ አማራጭ ማዘጋጀቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።
የዲጂታል አማራጮቹ፤ በስድስት የሀገሪቱ ቋንቋዎች ምዝገባ ለማከናወን እንዲችሉ ተደርገው መዘጋጀታቸውን ገልጿል። ይህ የዲጂታል የምዝገባ ሥርዓት በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ተግባራዊ የሚደረግ ነው።
ምርጫ ቦርድ በአጠቃላይ ካሉት 55 ሺህ ገደማ የምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ፤ በዲጂታል መንገድ የዕጩዎች እና የመራጮች ምዝገባን ለማከናወን ያቀደው 30 በመቶ ያህል በሚሆኑት ላይ እንደሆነ ዛሬ በተካሄደ ሥነ-ስርዓት ላይ ይፋ አድርጓል። አመልክቷል።
መራጮች ከዘንድሮው ምርጫ ጀምሮ ቋሚ የመራጭ ቁጥር እንደሚሰጣቸውም የምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ገልጸዋል። ይህ ቁጥር አንድ መራጭ ከሀገራዊ ምርጫ በተጨማሪ በህይወቱ ዘመን ሁሉ በሚሳተፍባቸው ማናቸውም በቦርዱ የሚመሩ ምርጫዎች ላይ ድምጽ መስጠት የሚያስችለው እንደሆነም ዋና ሰብሳቢዋ አስገንዝበዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
🔴 ዝርዝሩን በጹሁፍ ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2026/17050/
---------------------------------------------------------------------------------------------------------------------
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ http://ethiopiainsider.com
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
ቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopiaInsiderNews
ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: