በ“ስድብ እና ማዋረድ” ወንጀል በየዓመቱ “በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች” ተጠያቂ እየተደረጉ እንደሚገኙ የፍትህ ሚኒስትሯ ተናገሩ | Ethiopia Insider
Автор: Ethiopia Insider
Загружено: 2026-01-01
Просмотров: 14247
በእናቶች ላይ የሚፈጸም “ስድብ” ትኩረት ተሰጥቶት መፍትሔ እንዲፈለግለት አንድ የፓርላማ አባል ጠየቁ። ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በመወከል ከኦሮሚያ ክልል፣ ምሥራቅ ሐረርጌ ዞን፣ ደደር ምርጫ ክልል የተመረጡት ዶ/ር ኤልያስ አህመድ፤ ሁኔታው “የፈጣሪን ቁጣ እንዳያስከትል” ስጋታቸውን ገልጸዋል።
ዶ/ር ኤልያስ እናት የምትሰደብበት አስጸያፊ ቃላት “ከባዕድ ሀገር ወደ ምስራቅ ኢትዮጵያ” ቀጥሎም ወደሌሎች አካባቢዎች “እየተሰራጨ” መሆኑ እንደሚያሳስባቸው ዛሬ ሐሙስ ታኅሣሥ 23፤ 2018 በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ተናግረዋል። የዛሬው መደበኛ ስብሰባ አጀንዳ፤ የፍትህ ሚኒስትሯ ሃና አርዓያሥላሴ ከፓርላማ አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች የሚሰጡትን ምላሽ ማዳመጥ ነበር።
ይህንን ዕድል የተጠቀሙት ዶ/ር ኤልያስ፤ በእናቶች ላይ የሚፈጸም ስድብ ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይሰማ እና የእናትን ክብር በዘላቂነት ለማስከበር ፍትህ ሚኒስቴር ስለሚሰራቸው ስራዎች ጠይቀዋል። የፍትህ ሚኒስትሯ ለዚህ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፤ “ስድብና ማዋረድ” በኢትዮጵያ ብዙ የወንጀል ክስ የሚቀርብበት እና ተጠያቂነት የሚረጋገጥበት ጉዳይ እንደሆነ ተናግረዋል።
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ http://ethiopiainsider.com
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
ቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopiaInsiderNews
ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: