አዲስ አበባ 46ኛ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ልታገኝ ነው
Автор: Ethiopia Insider
Загружено: 2026-01-15
Просмотров: 64
ለአዲስ አበባ ከተማ በአሁኑ ወቅት አገልግሎት እየሰጡ ከሚገኙ 45 የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያዎች ተጨማሪ የሆነ ጣቢያ ግንባታ ከትላንት በስቲያ መጀመሩን የከተማይቱ ውሃና ፍሳሽ ባለሥልጣን አስታወቀ። ጣቢያው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ያሉትን የካ፣ ቦሌ እና ለሚ ኩራ ክፍለ ከተሞችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን መስሪያ ቤቱ ገልጿል።
በአዲስ አበባ ከተማ ካሉ የፍሳሽ ማጣሪያዎች ውስጥ በአቅሙ ትልቁ የሆነው ጣቢያ የሚገኘው በቃሊቲ ነው። በቀን 100 ሺህ ሜትር ኪዩብ ፍሳሽ ቆሻሻ ወይም ከ100 ሚሊዮን ሊትር በላይ ፍሳሽ ቆሻሻ የማጣራት አቅም ያለው ይህ ጣቢያ፤ ስራ የጀመረው በ2010 ዓ.ም ነበር።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ያወጣው የወንዞችን ብክለት ለመከላከል የሚያስችል ደንብ ፤ በአዲስ አበባ ከተማ ያሉ ወንዞችን በሚበክሉ ድርጅቶች ላይ እስከ አንድ ሚሊዮን ብር ቅጣት የሚጥል ነው። ከመኖሪያ ቤቶች የሽንት ቤት አሊያም ማንኛውንም ያልተጣራ ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ መልቀቅ ደግሞ በደንቡ መሰረት እስከ 300 ሺህ ብር ያስቀጣል።
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ http://ethiopiainsider.com
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
ቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopiaInsiderNews
ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: