#የአብይ
Автор: Aynalem የሚካኤል ልጅ ነኝ
Загружено: 2023-02-27
Просмотров: 733
የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት
[ ቅድስት ]
#" ቅድስት " ማለት ‹ የተለየች ፣ የነጻች ፣ የከበረች › ማለት ነው፡፡ ይኸውም ጌታችን ጾም የጀመረባት ፣ ልዩ ፤ የተቀደሰች ፤ የከበረች ፤ ልዩ ፣ ንጹሕ ፣ ክቡር በሚኾን በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጾመች መኾኗን ያመላክታል፡፡
ይህች ጾም በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ አራት የተገለጠችው የጌታችን ጾም ስትኾን ፣ ስያሜዋና የዕለቷ የምስጋና ሥርዓትም የቅዱስ ያሬድ ነው፡፡አምላካችን በገዳመ ቆሮንቶስ ዐርባ መዓልትና ዐርባ ሌሊት በጾመበት ጊዜያት እነዚህ ሦስቱን አርእስተ ኃጣውእ ድል አድርጓል፡፡
ሦስቱ አርእስተ ኃጣውእ የሚባሉትም ፦ ትዕቢት ፣ ስስትና ፍቅረ ንዋይ ናቸው፡፡ በእነዚህ ሦስት ኃጢአቶች ጌታችን በዲያሎስ በተፈተነ ጊዜ በትዕቢት ቢመጣበት በትሕትና ፤ በስስት ቢመጣበት በትዕግሥት ፤ በፍቅረ ንዋይ ቢመጣባት በጸሊዓ ንዋይ ጌታችን ዲያሎስን ድል አድርጎታል፡፡ ለእኛም እነዚህን ድል ለማድረግ የምንችልበትን ጥበብ – ጾምን ገልጦልናል፡፡
ትዕቢት ያልተሰጠንን መሻት ፣ ስስት አልጠግብ ባይነት ስግብግብ መኾን ፣ ፍቅረ ንዋይ ለገንዘብ ሲሉ ፈጣሪን መካድ ነው፡፡ አንደ ክርስቲያን ሦስቱን አርእስተ ኃጣውእ ድል ካደረገ ሌሎችን ኃጣውእ በቀላሉ ድል ማድረግ ይቻለዋል፡፡
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: