"ዳቺ " የታሸጉ የባቄላ እና ቦሎቄ ምርቶችን ኤክስፖርት ማድረግ ሊጀምር ነው‼️
Автор: ECN-TV
Загружено: 2026-01-16
Просмотров: 8
ዳቺ በኢትዮጵያ ውስጥ ሙሉ በሙሉ የተመረቱ የታሸጉ የባቄላ እና ቦሎቄ ምርቶችን ኤክስፖርት ማድረግ ሊጀምር መሆኑን የምግብ ማቀነባበርያ አክሲዮን ኩባንያ የሆነው ዳቺ ማኑፋክቸሪንግ አስታውቋል።
የዳቺ ምርቶች ከውጪ ገበያ በተጨማሪም ለሀገር ውስጥ ገበያ የሚያቀርብ እንደሆነ ተገልጿል። የድርጅቱ ኃላፊ አቶ ቢኒያም ዮሀንስ እንደተናገሩት በኢትዮጵያ ውስጥ ሙሉ በሙሉ የተመረቱ የታሸጉ የባቄላ እና ቦሎቄ ምርቶችን ማምረት ጀምሯል ።
የታሸጉ የባቄላ እና ቦሎቄ ምርቶቹን ከሀገር ውስጥ በተጨማሪ በቅርቡ ዱባይን ጨምሮ ወደ ዓለም አቀፍ ገበያዎችም የሚላኩ መሆናቸውን አስታውቋል ።
የታሸጉ የባቄላ እና ቦሎቄ ምርቶች ቀይ ቦሎቄን ነጭ ቦሎቄን፡ ጥቁር ቦሎቄን፣ ፉል፤ አተርን እና ጣፋጭ ቦሎቄን (Sweet Com) ያካትታሉ። ምርቶቹ በ400 ግራም መጠን የታሽጉ ሲሆኑ በጥቂት ወራት ውስጥ 3 ኪሎ ግራም መጠን ያላቸው እሽጎችም ለገበያ እንደሚቀርቡ ተናግረዋል።
ይህ መነሻ ኢትዮጵያን ከጥሬ ዕቃዎች ላኪነት ወደ ከፍተኛ እሴት ያላቸው፣ ዓለም አቀፍ የጥራትና የደህንነት መመዘኛዎችን የሚያሟሉ የተጠናቀቁ የምግብ ምርቶች ላኪነት የሚያሸጋግር ሂደት መሆኑን አመላክተዋል።
"አዳዲሶቹ ምርቶች ኢትዮጵያ በዓለም የምግብ አቅርቦት ሰንሰለት ውስጥ ያላት ሚና እየተቀየረ መሔዱን አብሳሪ ናቸው" በማለትም ተናግረዋል ።
ዳቺ የምግብ ኢንዱስትሪ አራት ፋብሪካዎችን የሚያስተዳድር የአክሲዮን ኩባንያ ነው። እነሱም የታሸገ ምግብ ፋብሪካ፡ የቲማቲም ድልህ ፋብሪካ፡ የፍራፍሬ ኮርዲያል፡ ጃምና ማዮኔዝ ፋብሪካ እንዲሁም የኮንዲመንት ፋብሪካ ናቸው። የኮንዲመንት ፋብሪካው ካችአፕ፣ ሶይ ሶስ፣ መስታርድ፣ የምግብ ቀለም እና ቫኒላን ጨምሮ 26 ዓይነት ምርቶችን ያመርታል።
#ECN-NEWS
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: