ሁሉ ከንቱ (መክብብ)
Автор: 12 Empty Jars Productions
Загружено: 2025-11-19
Просмотров: 638
በኢየሩሳሌም የነገሠ የሰባኪው
የዳዊት ልጅ ቃል።
ሰባኪው
“ከንቱ፥ ከንቱ፥
የከንቱ ከንቱ
ሁሉ ከንቱ ነው” ይላል።
ከፀሐይ በታች በሚደክምበት
ድካም ሁሉ
የሰው ትርፉ ምንድር ነው?
ትውልድ ይሄዳል፥
ትውልድም ይመጣል፤
ምድር ግን ለዘላለም ነው።
ፀሐይ ትወጣለች፥
ፀሐይም ትገባለች፥
ወደምትወጣበትም ስፍራ ትቸኩላለች።
ነፋስ ወደ ደቡብ ይሄዳል፥
ወደ ሰሜንም ይዞራል፤
ዘወትር በዙረቱ ይዞራል፥
ነፋስም በዙረቱ ደግሞ ይመለሳል።
ፈሳሾች ሁሉ ወደ ባሕር ይሄዳሉ፥
ባሕሩ ግን አይሞላም፤
ፈሳሾች ወደሚሄዱበት ስፍራ
እንደ ገና ወደዚያ ይመለሳሉ።
ነገር ሁሉ ያደክማል
ሰው ይናገረው ዘንድ አይችልም፤
ዓይን ከማየት አይጠግብም፥
ጆሮም ከመስማት አይሞላም።
ሰባኪው
“ከንቱ፥ ከንቱ፥
የከንቱ ከንቱ
ሁሉ ከንቱ ነው” ይላል።
የሆነው ነገር እርሱ የሚሆን ነው፥
የተደረገውም ነገር እርሱ የሚደረግ ነው፤
ከፀሐይም በታች አዲስ ነገር የለም።
ማንም
“እነሆ፥ ይህ ነገር አዲስ ነው”
ይል ዘንድ ይችላልን?
እርሱ ከእኛ በፊት በነበሩት ዘመናት ተደርጎአል።
ለፊተኞቹ ነገሮች መታሰቢያ የላቸውም፤
ለኋለኞቹም ነገሮች
ከእነርሱ በኋላ በሚነሡት ሰዎች ዘንድ
መታሰቢያ አይገኝላቸውም።
ሰባኪው
“ከንቱ፥ ከንቱ፥
የከንቱ ከንቱ
ሁሉ ከንቱ ነው” ይላል።
እኔ ሰባኪው በእስራኤል ላይ
በኢየሩሳሌም ንጉሥ ነበርሁ።
ከሰማይም በታች የተደረገውን ሁሉ
በጥበብ እፈልግና እመረምር ዘንድ
ልቤን አተጋሁ፤
እግዚአብሔር ይደክሙባት ዘንድ
ይህችን ለሰው ልጆች የሰጠ ክፉ ጥረት ናት።
ከፀሐይ በታች የተሠራውን
ሥራ ሁሉ አየሁ፤
እነሆም፥ ሁሉ ከንቱ ነው፥
ነፋስንም እንደ መከተል ነው።
ጠማማ ይቀና ዘንድ አይችልም፤
ጎደሎም ይቆጠር ዘንድ አይችልም።
ሰባኪው
“ከንቱ፥ ከንቱ፥
የከንቱ ከንቱ
ሁሉ ከንቱ ነው” ይላል።
እኔ በልቤ
“እነሆ፥ ከእኔ አስቀድመው
በኢየሩሳሌም ላይ ከነበሩት ሁሉ ይልቅ
ጥበብን አብዝቼ ጨመርሁ፤
ልቤም ብዙ ጥበብንና እውቀትን ተመለከተ” ብዬ ተናገርሁ።
ጥበብንና ዕብደትን ሞኝነትንም
አውቅ ዘንድ ልቤን ሰጠሁ፤
ይህም ደግሞ ነፋስን እንደ መከተል
እንደ ሆነ አስተዋልሁ።
በጥበብ መብዛት ትካዜ ይበዛልና፤
እውቀትንም የሚጨምር ኀዘንን ይጨምራልና።
ሰባኪው
“ከንቱ፥ ከንቱ፥
የከንቱ ከንቱ
ሁሉ ከንቱ ነው” ይላል።
ሰባኪው
“ከንቱ፥ ከንቱ፥
የከንቱ ከንቱ
ሁሉ ከንቱ ነው” ይላል።
Ethiopian Music, New Ethiopian Music, Ethiopian and Eritrean Music
Mezmur
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: