#የታሕሣሥ
Автор: kesisephrem
Загружено: 2025-12-16
Просмотров: 63
ስንክሳር ዘወርኀ ታኅሣሥ 8
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ስምንት በዚች ቀን የእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ቅዱስ አባት አባ ያሮክላ አረፈ እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ዐሥራ ሦስተኛ ቊጥር ነው ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ አስቀድሞ አረማውያን ነበሩ በወለዱትም ጊዜ የአረማውያንን ትምህርት መጻሕፍቶቻቸውንም ሁሉ አስተማሩት ።
ከዚህም በኋላ አምነው ተጠመቁ ይህን ልጃቸውንም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተማሩት የሐዋርያትንም መጻሕፍት አጠና ሊቀ ጳጳሳት ድሜጥሮስም ዲቁና ሾመው ከዚህም በኋላ በእስክንድርያ አገር ቤተ ክርስቲያን ቅስና ሾመው መንጋውንም በመልካም አጠባበቅ ጠበቀ ።
ሥራውንም ፈጸመ የቤተ ክርስቲያንንም ሕግ ጠንቅቆ አወቀ ። አባት ድሜጥሮስም በአረፈ ጊዜ ይህን አባት መርጠው በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት እርሱም ክብርይግባውና የክርስቶስን መንጋዎች በቀናች ሃይማኖት አጽንቶ ጠበቀ ከአረማውያንም ብዙዎችን ክብር ይግባውና ክርስቶስን ወደ ማመን መልሶ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው ።
ለቅዱስ ዲዮናስዮስም ለምእመናን እንዲፈርድ ሥልጣን ሰጠው እርሱ ግን ዓላው ያንን ወደ ቀናች ሃይማኖት
እስከሚመልሳቸው ድረስ ያስተምራቸውና ይገሥጻቸው ነበር ። በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበርም ዐሥራ ሦስት ዓመት ኑሮ በሰላም አረፈ ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።
በዚችም ቀን የከበሩ ሴቶች በርባራና ዮልያና በሰማዕትነት አረፉ ። ይችም ቅድስት በርባራ በከሀዲው መክስምያኖስ ዘመነ መንግሥት በቤተ መንግሥት ውስጥ ታላቅ መስፍን ለሆነ ሰው ልጁ ናት ስሙም ዲዮስቆሮስ ነው እርሱም ለልጁ ለበርባራ ማንም እንዳያያት ታላቅ ጽኑ የሆነ ሕንፃ አሠራ ከዚህም ዳግመኛ መታጠቢያ የውሽባ ቤት በግንብ ሠራ የሚከፈቱ ሁለት መስኮቶችንም በውስጡ እንዲሠሩ አዘዘ ። ቅድስት በርባራም ሁለቱን መስኮቶች በአየች ጊዜ ሦስተኛ መስኮትን እንዲሠሩ ሐናፂዎችን አዘዘቻቸው ከዚህም በኋላ ክብርይግባውና የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አዳኝ የሆነ የመስቀሉን ምልክት በውኃ መታጠቢያው ላይ አሠራች ።
አባቷም ወደዚህ ሕንፃ በገባ ጊዜ ይህን ልጁ ያሠራችውን አይቶ አናፂዎችን ጠየቀ እነርሱም ይህን እንድንሠራ ልጅህ አዘዘችን አሉት እርሷንም ጠርቶ ለምን እንዲህ አደረግሽ አላት ። እርሷም አባቴ ሆይ አስተውል ልዩ ሦስት በሆነ በሥላሴ ስም ሥራ ሁሉ ይፈጸማልና ስለዚህ ሦስተኛ መስኮት አሠራሁ ይህም መስቀል ዓለሙ ሁሉ በእርሱ በዳነበት በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል አምሳል ነው አንተም አባቴ ሆይከስሕተትህ ተመልሰህ የፈጠረህን አምላክ አምልከው አለችው
አባቷም ከእርሷ ይህን በሰማ ጊዜ ሰይፉን መዝዞ በኋላዋ ሮጠ እርሷም ሸሸች በፊቷም የነበረች ዐለት ተሠንጥቃ በውስጧ ገብታ ሠወረቻት ። ከዚህም በኋላ ወደ አባቷ ተመለሰች እርሱም እንዲአሠቃያት ለሌላ መኰንን አሳልፎ ሰጣት እርሱም ታላቅ ሥቃይን አሠቃያት በዚያም ዮልያና የምትባል ሴት ነበረች ቅድስት በርባራንም አየቻትና የምታጽናናትና የምታረጋጋት ሆነች ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ለቅድስት በርባራ ተገለጸላትና አረጋጋት ።
ከዚህም በኋላ አባቷ በሰይፍ ራሷን እንዲቆርጡ የባልንጀራዋ የዮልያናንም ራስ እንዲቆርጡ አዘዘና ቆረጧቸው የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበሉ ። በዚያንም ጊዜ ከሰማይ እሳት ወርዶ አባቷንና ጓደኛው የሆነ መኰንን መርትያኖስን አቃጠላቸው ያም በውሽባ ቤት ውስጥ በመስቀል ምልክት ያሠራቸው መታጠቢያ ለታመመ ሁሉ ከእርሱ በታጠበ ጊዜ የሚያድን በውስጡ ታላቅ ፈውስ ያለበት ሆነ ።
ከዚህም በኋላ የቅዱሳት ሰማዕታትን ሥጋቸውን ወስደው ከከተማ ውጭ ባለች ቤተ ክርስቲያን ስሟ ገላልያ በሚባል ቦታ አኖሩአቸው ይህ ሥጋቸውም በቅዱሳን ሰማዕታት በአቡቂርና በዮሐንስ በምስር አገር በአለ ቤተ ክርስቲያናቸው እስከ ዛሬ አለ ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳት ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።
በዚችም ቀን የደብረ ድማሕ ገዳም አበምኔት ቅዱስ አባት ተክለ አልፋ አረፈ ። ዳግመኛም በክርስቶስ የሚታመን የገብረ ማርያም ዕረፍቱ ነው እርሱም የሰማዕታትንና የጻድቃንን በየዕረፍታቸው ቀን ለየአንዳንዱ ርኁባንን በማጥገብ የተራቆቱትን በማልበስ መታሰቢያቸውን የሚያደርግ ነው ።
እንዲህም ባለ ሥራ ላይ እያለ ያንጊዜ እስላሞች ወደ ሸዋ አገር መጡ እርሱም ያማሩ ልብሶችን ለብሶ ወደ ቤተክርስቲያን ሔዶ ገብቶ ጸሎትን ጸለየ ሲጸልይም እስላሞች ወደርሱ መጥተው ራሱን በሰይፍ ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ሁሉ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።
ታኅሣሥ ፰ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
፩.ታላቁ አቡነ ኪሮስ
፪.አባ ሳሙኤል ዘደብረ ቀልሞን
፫.አባ ዮሐንስ ዘደማስቆ ሊቁ
፬.አባ ኤሲና ቅድስት ቴክላ
፭.ቅዱሳት በርባራና ዮልያና
፮.ቅድስት እንባ መሪና
፯.አባ ተክለ አልፋ ዘደብረ ድማሕ
፰.ቅዱስ ገብረ ማርያም ተአማኒ
፱.አባ ያሮክላ ሊቀ ጳጳሳት
፲.አቡነ እስትፋሰ ክርስቶስ ልደታቸው
ወርኀዊ በዓላት
፩.ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት
፪.አባ ብሶይ ቢሾይ
፫.ቅዱሳን ፬ቱ እንስሳ ኪሩቤል
፬.ቅዱስ ማትያስ ሐዋርያ ከ፲፪ቱ ሐዋርያት
እግዚአብሔር ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ: እስከ አሁንም ስለምታገለግሏቸው
ያደረጋችሁትን ሥራ: ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመጸኛ አይደለምና ። በእምነትና በትእግስትም የተስፋውን ቃል የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንዳትሆኑ ... ዕብ. ፯፥፲
Доступные форматы для скачивания:
Скачать видео mp4
-
Информация по загрузке: